|
የጥናትና ምርምር ማእከሉ ሁለተኛ ዓመታዊ ዐውደ ጥናቱን ሊያካሔድ ነው |
|
በተ/ሥላሴ ጸጋ ኪሮስ
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን ጥናትና
መርምር ማእከል ሁለተኛ ዓመታዊ ዓውደ ጥናቱን ከነሔሴ 29 እስከ 30 ቀን 2002 ዓ.ም ያካሒዳል፡፡
|
|
ተጨማሪ ያንብቡ...
|
|
|
የውጭ ማእከላት ሳምንት በሚል ርዕስ የተዘጋጀው ዓውደ ርእይ ነገ ይከፈታል |
|
በተ/ሥላሴ ጸጋ ኪሮስ
በማኅበረ ቅዱሳን የውጭ ማእከላት ማደራጃና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀው ዐውደ ርእይ ከነሐሴ 28 እስከ 30 ቀን 2002 ዓ.ም ይካሔዳል፡፡ የውይይት መርሐ ግብርም ተዘጋጅቷል።
በዋናው ማእከል ሕንፃ ላይ የሚካሔደው ዓውደ ርእይ ከኢትዮጵያ ውጭ ያለውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ
ክርስቲያን እና የማኅበረ ቅዱሳንን እንቅስቅሴ በዋነኝነት ሲመለከት ያጋጠሙ ችግሮችንም ይዳስሳል፡፡ በተጨማሪም
በየአህጉራቱ ያለውን የአኀት አብያተ ክርስቲያናት እንቅስቅሴ፣ የማኅበረ ቅዱሳን የውጭ ማእከላት ማደራጃና
ማስተባበሪያ ዋና ክፍል ተግባራት፣ ራእይና ዓላማ ይዳሰስበታል፡፡
|
|
ተጨማሪ ያንብቡ...
|
|
|
የማኅበረ ቅዱሳን ዘጠነኛ ጠቅላላ ጉባኤ ተጠናቀቀ |
|
በተ/ሥላሴ ጸጋ ኪሮስና ኪ/ማርያም
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን ዘጠነኛ
ጠቅላላ ጉባኤ የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ተጠናቀቀ፡፡ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይም ውይይት ተካሂዷል ፡፡
|
|
ተጨማሪ ያንብቡ...
|
|
|
«የጻድቅ ሞት በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው።» መዝ 115፥6 |
|
ይህንን ቃል የተናገረው ልበ አምላክ ክቡር ዳዊት ነው፡፡ ሞት ለአዳማውያን ሁሉ የማይቀር ከጨለማ ወደ ብርሃን፣
ከጠባብ ወደ ሰፊ፣ ከጊዜያዊ ወደ ዘላለማዊ የሚሸጋገሩበት ድልድይ ነው፡፡ ቁም ነገሩ ግን በሃይማኖት በምግባር
ጸንቶ ገድል፣ ትሩፋትን ፈጽሞ፣ የክብርን አክሊል ተቀዳጅቶ በረከትንና ቃል ኪዳንን ተቀብሎ መጠራት የዘላለም ጸጋ
የሚያስገኝ ነው፡፡ እንዲህ ዓይነትን ሞት ነው ክቡር ዳዊት «የቅዱሳን ሞት በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው»
ያለው፡፡ ለዚህ ክብር ከበቁ ቅዱሳን አንዱ አባታችን አቡነ ተክለሃይማኖት ናቸው።
|
|
ተጨማሪ ያንብቡ...
|
|
|