የእለቱ ጥቅስ

እስከ ሞት ድረስ የታመንህ ሁን - ራዕ. 2.10

Site Last Updated:-Friday 3 September 2010
ዜና
የጥናትና ምርምር ማእከሉ ሁለተኛ ዓመታዊ ዐውደ ጥናቱን ሊያካሔድ ነው
በተ/ሥላሴ ጸጋ ኪሮስ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን ጥናትና መርምር ማእከል ሁለተኛ ዓመታዊ ዓውደ ጥናቱን ከነሔሴ 29 እስከ 30 ቀን 2002 ዓ.ም ያካሒዳል፡፡
ተጨማሪ ያንብቡ...
 
የውጭ ማእከላት ሳምንት በሚል ርዕስ የተዘጋጀው ዓውደ ርእይ ነገ ይከፈታል
በተ/ሥላሴ ጸጋ ኪሮስ

በማኅበረ ቅዱሳን የውጭ ማእከላት ማደራጃና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀው ዐውደ ርእይ ከነሐሴ 28 እስከ 30 ቀን 2002 ዓ.ም ይካሔዳል፡፡ የውይይት መርሐ ግብርም ተዘጋጅቷል።

በዋናው ማእከል ሕንፃ ላይ የሚካሔደው ዓውደ ርእይ ከኢትዮጵያ ውጭ ያለውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እና የማኅበረ ቅዱሳንን እንቅስቅሴ በዋነኝነት ሲመለከት ያጋጠሙ ችግሮችንም ይዳስሳል፡፡ በተጨማሪም በየአህጉራቱ ያለውን የአኀት አብያተ ክርስቲያናት እንቅስቅሴ፣ የማኅበረ ቅዱሳን የውጭ ማእከላት ማደራጃና ማስተባበሪያ ዋና ክፍል ተግባራት፣ ራእይና ዓላማ ይዳሰስበታል፡፡
ተጨማሪ ያንብቡ...
 
የማኅበረ ቅዱሳን ዘጠነኛ ጠቅላላ ጉባኤ ተጠናቀቀ
በተ/ሥላሴ ጸጋ ኪሮስና ኪ/ማርያም

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን ዘጠነኛ ጠቅላላ ጉባኤ የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ተጠናቀቀ፡፡ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይም ውይይት ተካሂዷል ፡፡  

general_assembly.jpg

 

 

 

 

 

ተጨማሪ ያንብቡ...
 
የማኅበረ ቅዱሳን 9ኛው ጠቅላላ ጉባኤ ተከፈተ
 
በተ/ሥላሴ ጸጋ ኪሮስ

 የማኅበረ ቅዱሳን 9ኛው ጠቅላላ ጉባኤ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ ፥ ብፁአን ሊቃነ ጳጳሳት፥ የጠቅላይ ቤተ ክህነት የመምሪያ ኃላፊዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በጸሎት በይፋ ተከፈተ። የማኅበረ ቅዱሳን የሁለት ዓመት ክንውን ሪፖርት ቀርቧል።

2002teklala_gubaea.jpg
ተጨማሪ ያንብቡ...
 
“በምንት ያረትዕ (ማኅበረ ቅዱሳን) ወሬዛ ፍኖቶ? በአቂበ ነቢብከ ፥ በአቂበ ትእዛዝከ።» መዝ 118፥9
በተ/ሥላሴ ጸጋ ኪሮስና በኪ/ማርያም
 
የማኅበረ ቅዱሳን ጠቅላላ ጉባኤ የእንኳን ደህና መጣችሁ መክፈቻ መርሐ ግብር ዛሬ አርብ ነሐሴ 21፣ 2002 ዓ.ም ተካሄደ። በነገው ዕለት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተ/ሃይማኖት የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት ፕሬዚዳንት የዓለም ሃይማኖቶች ምክር ቤት ለሰላም የክብር ፕሬዚዳንት በሚገኙበት ጉባኤው በጠቅላይ ቤት ክህነት አዳራሽ በይፋ ይከፈታል።
ተጨማሪ ያንብቡ...
 
<< መጀመሪያ < ወደኋላ 1 2 3 4 5 6 7 8 9 10 ወደፊት > መጨረሻ >>

ውጤቶች 1 - 9 ከ 115
Difficulty with characters ?
Click here! if you have difficulty reading amharic(geez) characters
ያግኙን
አስተያየት፤ ጥያቄ ወይም ጥቆማ ካለዎት እዚህ ይጫኑ።
ምን ተለወጠ ?