|
ሰኔ 6 ቀን 2005 ዓ.ም.
በአብርሃም ቸርነት/ዘገዳመ ኢየሱስ/
ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ በተነሣ በአርባኛው ቀን ቅዱሳን ሐዋርያት በጸሎት ይተጉ ወደነበረበት ቤት በመሄድ ደቀመዛሙርቱን ይዟቸው ከቤት በመውጣት መንገድ ጀመረ፡፡ እርሱ ከፊት ከፊት እየመራቸው እነርሱ እየተከተሉት ወደ ረጅሙና በረጃጅም ዛፎች ወደ ተሞወው ደብረ ዘይት ተራራ ይዟቸው ወጣ፡፡
|
|
ዝርዝር ንባብ...
|
|
|
ለ.1 ግእዝ ምስለ ቤተ ክርስቲያን ቤተ ክርስቲያን ለብዙ ዘመናት የፈተና ገፈታ ቀማሽ በመሆን፣ ልጆቿን እያበረታታች ለሀገራዊ ሀብት መጠበቅም እስከ ሰማዕትነት እያበረከተች በየአድባራቱና ገዳማቱ ጠብቃ አሳድጋ ለዚህ ትውልድና ዘመን ካቆየቻቸው ዕሤቶች አንዱ ግእዝ ነው፡፡ ቤተክርስቲያን ቤተ መዘክር፣ ቤተ ክርስቲያን ትምህርት ቤት፣ ቤተ ክርስቲያን ግምጃ ቤት፣ ቤተክርስቲያን የሥልጣኔ ማዕከል፣ ቤተ ክርስቲያን ከተማ ሀገር በመሆን ስታገለግል ቆይታለች፡፡
|
|
ዝርዝር ንባብ...
|
|
በዓለም የሥነ ልሳን ጥናት መሠረት የአካድ /የአሦር - አካዳውያን/ ቋንቋ ጥንታዊ ማንነቱ የተረጋገጠው በአንዳንድ የሥነ ጽሑፎች ቅሪት ሲሆን ይህ ቋንቋ በሥነ ልሳን ተማራማሪዎች ዘንድ የምሥራቅ ሴማዊ ልሳን ተብሎ በቅርብ ጊዜ ከተገኘው ከኤብላዊ ቋንቋ ጋር የሚመደብ ነው፡፡ አካድ እና አሦር በመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል በኦሪት ዘፍጥረት የተገለጹ እና ከኖኅ ዘመን በኋላ የታወቁ መካናተ ሥልጣኔ ናቸው፡፡ በሥነ ጽሑፍ መረጃ የአከድ ልሳን 2500 ቅ.ል.ክ. እንደነበረ ይናገራል፡፡ በኋላ በአራም የአራማውያን የተባለው ቋንቋው ራሱን የገለጸበት ጊዜ ነበር፡፡ ይሁን እንጂ በሥነ ቅሬተ ምድርም ሆነ በሥነ ልሳን ተመራማሪዎች ዘንድ አካድ የኢኮኖሚ፣ የሕግ የአስተዳደር፣ የታሪክና የሥነ ጽሑፍ መረጃዎች እንደነበረው የተረዳ ነው፡፡
|
|
ዝርዝር ንባብ...
|
|
ግንቦት 16/2004 ዓ.ም.
“አልቦ ዘዐርገ ውስተ ሰማይ ዘእንበለ ዘወረደ እምሰማይ ወልደ እጓለመሕያው” ዮሐ.3፥13

ከሰማይ ከወረደው የሰው ልጅ በቀር ወደ ሰማይ የወጣ የለም፡፡ እርሱም በሰማይ የሚኖረው ነው፡፡ ይህ ኃይለ ቃል ክብር ምስጋና ይግባውና ስለጌታችን፣ አምላካችን፣ መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሰማየ ሰማያት መውረድ ከድንግል ማርያም መወለድ እና የሰውነቱን ሥራ ጨርሶ በክብር ወደ ሰማይ ማረጉን የሚገልጽ ነው፡፡ እንደሚታወቀው አምላካችን ስለሁለት አቢይ ጉዳዮች ሰው ሆኗል፡፡
- ለቤዛነት /ዓለምን ለማዳን/
- ለአርአያነት /ምሳሌነት/
|
|
ዝርዝር ንባብ...
|
|
በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሚታየውን የአሠራር ብልሹነት ማሰወገድ እንደሚገባ ተገለጸ |
|
ሰኔ 6 ቀን 2005 ዓ.ም.
በትዕግሥት ታፈረ
በቤተ ክርስቲያን አስተዳደር ውስጥ የሚታየውን የአሠራር ብልሹነት ማሰወገድ እንደሚገባ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖትና ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ገለጹ፡፡
ቅዱስነታቸው ይህንን የገለጹት በግንቦቱ ርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ባስተላለፈው ውሳኔ መሠረት የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፤ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፤ እንዲሁም የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ሆነው የተመረጡት ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ከጠቅላይ ቤተ ክህነት ሓላፊዎችና ሠራተኞች ጋር ሰኔ 4 ቀን 2005 ዓ.ም. የትውውቅ መርሐ ግብር በተካሄደበት ወቅት ነው፡፡
|
|
ዝርዝር ንባብ...
|
|
|
|
|
<< ጀምር < ወደኋላ 1 2 3 ወደፊት > መጨረሻ >>
|
|
ገጽ 1 ከ 3 |